Detecting...

Please whitelist dirzon to continue.

or subscribe for ad-free contenct.

dirzon
  • Convert to Pdf
  • Reading List
  • Summary
  • Audiobook
  • Search
  • Upload
  • myzon
  • Log in
  • Register
English  አማርኛ  Français  العربية
Book of the day

አላህን የመውደድ ሚስጢር ሀሰን ታጁ (1).pdf


  • word cloud

አላህን የመውደድ ሚስጢር ሀሰን ታጁ (1).pdf
  • Extraction Summary

ኀጎ ቦያመውደድ ፖነሃህጪረ በዑስማን ኑሪ ቶኘባሽ ትርጉም አህመድ ሁሴን አቡ ቢላል አርትኦት ሐሰን ታጁ ቆታሟ ለኋጳጩዖ ሊሚትድ ኃሳያ ወፖረ ዐፀ « መዉደም ዐዐ ፀ« ፅዳያ ለያ ዲፈጉሥሑ የአሳታሚው መብት በሕግ የተጠበቀ ነው። የሚያምርና ፍልቅልቅ ልጅ በውፃ ፈንታ አኮሌውን አንቆ ወደ መሬት ሲወጣ የተጠማው ሰው ጥሙን በመርሳት ፈዞ ቀረ ይሁን እንጂ ልጆቻችንን ከተለያዩ አደጋዎች ልንጠብቃቸው የምንችለው እንዴት ነው። እኔ አላህን የማመልከው በታላቅ ጥንቃቄ ነው ልቤ በአላህ ፍራቻ የተሞላ ስለሆነ ድካምም ሆነ በሰውነቴ ላይ የሚደርስ ነገር አያሳስበኝም ስለሆነም ሌሊቱ ረዥም አይሆንብኝም ኹሹዕ የሚባለው ነገርስ ምንድን ነው የምታደርጉት። አሉት ያዘዙትን ሁሉ ፈጸመ። አልቀለም የነብዩ ሰዐወ ባልደረቦች ከነበሩት የሶፃባ ትውልድ አባላት መካከል ከዘጠና በመቶ በላይ የሚሆኑት ኢስላምን የተቀበሉት በሚያስተምሯቸው የሞራል ምጥቀት ተስበው ነበር ጥቂቶቹ ለነቢዩ ሰዐወ ግልጽ የሆነ የጠላትነት ስሜትን ያንፀባርቁ የነበሩ ቢሆንም ውሸታም አምባገነን ወዘተ በማለት አይከሷቸውም ነበር። በአንድ ጥልቅ ጉድጓድ ውስጥ ወድቆ የገባን ሰው ብታዩ ምን ታደርጉ ነበር። ነጋሪ ሪሻ ተፀፅቶ የተመለሰና ያመነ መልካምን ሥራ የሰራ ሰው ብቻ ሲቀር አነዚያም አላህ መጥፎ ሥራዎቻቸውን በመልካም ሥራዎች ይለውጣል አላህም እጅግ መሐሪ አዛኝ ነውና አልሑጁራት የሄ ዕ የአላህ መልእክተኛም ሰዐወ እንዲህ በማለት ጠየቁት በአንተ ቦታ ሙሐመድ ቢሆንና አንተ ነፍስህን ብታተርፍ ይህን ትቀበላለህን።

  • Cosine Similarity

ሯፀዚቨርበ አዕዐህ ማውጫ ርእስ መግቢያ ምዕራፍ አንድ አላህን የመውደድ ምስጢር ምዕራፍ ሁለት ስብእናው የተሟላ ሰው ምፅራፍ ሶስት በአላህ መንገድ ላይ መጽናት ምዕራፍ አራት ከሷሊሆች እና ከእውነተኞች ጋር መሆን ምዕራፍ አምስት መሷጓም ሥታ ያቃታታ ረጴ ቹ መዕራሥ ምዕራፍ ስድስት አላህን መፍራትና እዝነቱንም ተስፋ ማድረግ ምዕራፍ ሰባት ግድየለሽነት ምዕራፍ ስምንት ወደ አላህ መቃረብ ምዕራፍ ዘጠኝ ሪዝቅ ሲሳይ ምዕራፍ አሥር ብርፃንና ጨለማ ምዕራፍ አስራ አንድ ኢህሳን ማሳመር እና ሙራቀባህ ገጽ ርእስ ምዕራፍ አሥራ ሁለት የሰውን ልጅ የሚመለከቱ አውነታዎች ምዕራፍ አሥራ ሦስት ከራስ ይልቅ ሌሎችን ማስቀደም አልኢሣር ምዕራፍ አሥራ አራት ኢስላም ለሰው ልጆች ሕይወት ይለግሳል ምዕራፍ አሥራ አምስት የጸባይ ታላቅነትና ውስጥን ማጽዳት ምዕራፍ አሥራ ስድስት አላህንና መልእክተኛውን ሰዐወ መውደድ ገጽ መግቢያ በአላህ ስም አጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው አላህን መውደድ የእምነት አስኳል የበጎ ስራዎች ሁሉ መሠረት እንደሆነ በቁርአንና በሐዲስ ተገልዷል መልእክተኛውን መውደድ ደግሞ አላህን የመውደድ መገለጫ ነው አላህ በቁርአኑ የአማኞችን ባህሪ ሲገልጽ እነቢያ ያመኑት ለአላህ የበረታ ፍቅር አላቸው አክል በቀራና አላህን የመውደድ ዋነኛ ማሣያ ነቢዩን መውደድና መከተል መሆኑን አላህ እንዲህ ሲል ይነግረናል አላህን የምትወዱ አንደሆናችሁ ተከተሉኝ አላህ ይወዳችልና በል አል ኢምራን ነቢዩ ሙሐመድ አርሳቸውን ከንብረቱ ከቤተሰቦቹና ከራሱም በላይ ያልወደደ ኢማኑ ሙሉ አንዳልሆነ ተናግረዋል የዚህ ፍቅር ሚስጥር መላ ሕይወትን ይቀይራል አእምሮን ያስተካክላል ቀልብን ንጹህና ቅን ያደርጋል ነፍስያን ይገራል ይህ ሲሆን የሰውየው ባህሪ ፍጹም ይለወጣል ለአላህም ለፍጡራኑም የሚመች ስብእና ይኖረዋል ሁሉን አፍቃሪ ለሁሉም ቅን አሳቢ የአላህ ቤተሰቦች ለሆኑት አዛኝና ጠቃሚ ይሆናል እንዲህ ዓይነት ስብእናዎች ሲበዙ አለም በፍቅር እና መተሳሰብ ትደምቃለች ወንድም በወንድሙ ላይ የሚጨክንበት ሂደት ያበቃል ቱርካዊው አሊም ሸኽ ዑስማን ኑሪ ቶኘባሽ የአላህን ፍቅር ትርጉምና መገለጫዎች በተዋበ ብዕርና የገለጻ ስልታቸው በዚህ መጽሐፍ ውስጥ አብራርተውልናል ለትምህርታቸው ተጠቃሚ ያደርገን ዘንድ አላህን እንለምናለን ሐሰን ታጁ ሕዳር ምዕራፍ አንድ አላህን የመውደድ ምስጢር በሰማያትና በምድር አንዲሁም በመካከላቸው ያሉ ፍጡራንን ሁሉ ካልነበሩበት ያስገኘው አላህ የሰው ልጅን ሲፈጥር ድንቅና ይህ ይቀረዋል የማይባለውን ችሎታውን ተጠቅሞ ነው ይህንንም ሲያደርግ ለታላቅ ዓላማ ሲሆን ይኸውም እርሱን እንደሚገባው አድርጎ እንዲገዛው ነው የሰው ልጅ ይህን የተጻፈለትን ግብ ሲከውን ግን አቅሙ በፈቀደው ያክል ፍቅርን ለብሶ ቢያደርገው ይበልጥለታል የዚህ ዓለም የመፈጠር ዋነኛው ግብም ለሚያማምሩና አይንን አፍዝዘው ለሚያስቀሩ ልምላሜ የሞላባቸው ሜዳዎች ሸለቆዎች ተራሮችና ወንዛወንዞች ታስቦ አይደለም ይህ ሁሉ የሆነው በዓለም ላይ ሰፍሮ ከዘመናት የጊዜ ማህጸን ውስጥ ዝርያዎቹን እያባዛና እየበዛ ለመጣውና በፈጣሪው ሞገስ ለተቸረው ለሰው ልጅ ተብሎ ነው አንግዲህ የፍጥረት ሁሉ አስገሺ የሆነው አላህ ይህን አለም ሲፈጥረውም ሆነ ሲያስተናብረው በታላቅ ፍቅርና እዝነቱ በማካበብ ነው ይህን ምስጢር መርምሮ ለማግኘት ሊቅነትን የማይጠይቅ ሲሆን ጊንጥ የፈለፈለቻቸውን አምሳያዎቿን በጀርባዋ አዝላ መታየቷን ማስተዋል ብቻ በቂ ነው ይህ በፍቅርና በመተዛዘን ስሌት ላይ የመሠረተ የፍጡራን ዝንባሌ ይበልጥ ጎልቶ የሚታየው በክቡሩ የሰው ልጅ ስብእናና ማህበራዊ ተራክቦ መሆኑ ይበልጥ ያስደንቃል የሆነ ሆኖ የው ዘር በዚህች ዓለም በሚቆይባቸው ዘመናቱ ብዙ ፈተናዎችንና የመከራ ቀንበሮችን መሸከም ቢኖርበትም እንኳ አነዚህን ሁሉ አበሳዎች የፈጣሪውን ውዴታና ፍቅር በመሻት እስከተጋፈጣቸው ድረስ ፈተናውን ወድቋል አይባልም ምክንያቱም የሚከፈለው ምንዳ ታላቅ የሆነ የፍቅር መገለጫ ሲሆን ተከትሎት የሚመጣው ዘውታሪ ፀጋም አማላይ ነውና የሰው ልጅ ልቦና ሲፈጠር ጽንፍ አልባ የሆነ የፍቅር ማህደር አንዲሆን ተደርጎ ነው ይህ ተፈጥሮው ከተሟላ ደረጃ ላይ የሚደርሰው ዝንባሌው አላህን ወደማፍቀር ካዘመመ ነው ይህን ሳያደርግ ቀርቶ ስሜቱንና ደመነፍሱን ተከትሎ ባፈተተው የሚነጉድ ከሆነ ግን ሕይወቱ ትርጉም አልባ ጉዞዋን አገባድዳ በሃዘን ታሳርጋለች በሌላ አገላለጽ ሰው የዘራውን ነውና የሚያጭደው በአላህና መልእክተኛው ሰዐወ ፍቅር ልቡ ያንጠና ይህንኑም በሕይወት ዘመናቱ በተግባር ለመግለጽ ደፋ ቀና ያለ በልፋቱና በድካሙ ልክ መልካም ምንዳውን ማግኘቱ አይቀሬ ነው በአላህ አእዝነት እርግጥ ነው ለሰማያትና ለምድር እንዲሁም ለተራሮች እንደሚከብድ በኃያሉ አላህ የተገለጸው አደራ አማና የሰው ልጅ ቢወድም ባይወድም ይሸከመው ዘንድ በጫንቃው ላይ ተጭናበታል ይህም በመሆኑ የሰው ነፍስ ጥንቱኑ ስትሰራ ለመልካምም ሆነ ለእኩይ ዝንባሌ ተገርታ ነው ይህንንም በማስመልከት ኃያሉና ጥበበኛው አላህ በቁርዓኑ እንደሚከተለው ይናገራል ሠ ሥ ዕጩ ይ ን ሽ። በእርሱ በአላህ ምንንም ነገር አታጋሩ ለወላጆችም በጎን ሥራ ሥሩ ልጆቻችሁንም በድህነት ፍራቻ አትግደሉ አኛ እናንተንም እነርሱንም እንመግባችኋለንና መጥፎ ሥራዎችንም ከርሷ የተገለጸውንም የደበቀውንም ሁሉ አትቅረቡ ያችንም አላህ እርም ያደረጋትን ነፍስ በሕግ ቢሆን እንጂ አትግደሉ ይኻችሁ ታውቁ ዘንድ አላህ በርሱ አዘዛችሁ የየቲምንም ገንዘብ ብርታቱን አካለ መጠን እስኪደርስ ድረስ በዚያች እርሷ መልካም በሆነች ሁኔታ እንጅ አትቅረቡ ስፍርንና ሚዛንንም በትክክሉ ምሉ ነፍስን ችሎታዋን እንጂ አናስገድድም በተናገራችሁም ጊዜ በዘመዶቻችሁ ላይ ቢሆንም እንኳን እውነቱን በመናገር አስተካክሉ በአላህም ቃል ኪዳን ምሉ ይኻችሁ ትገሰጹ ዘንድ በርሱ አዘዛችሁ ይህም ቀጥተኛ ሲሆን መንገዴ ነው ተከተሉትም የጥምመት መንገዶችንም አትከተሉ ከቀጥተኛው መንገድ እናንተን ይለያዩዋችልና ይኻችሁ ትጠነቀቁ ዘንድ በርሱ አዘዛችሁ አል አንአም የሰው ልጅ ቀናውን ጉዳና በትክክል አይመራም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ያለው ፍቅር ለሌሎች ነገሮች ካለው ፍቅር የበለጠ ሆኖ እስካልተገኘ ድረስ ይህንንም ለማድረግ የአላህን ታላቅነት ማወቅ የሚገባውን ያህል ማወቅ ይኖርበታል ምክንያቱም ሰዎች አላህን ማወቅ የሚገባቸውን ያክል ካላወቁት እንደሚገባው አድርገው ሊገዙት አይችሉምና እንዲሁም ከሰይጣን ወጥመድና ከሚያሳድረውም አፍራሽ ተጽዕኖ ለመጠንቀቅ የአላህን ብቸኛ የኃይል ባለቤት መሆን ማወቁ ጠቃሚ ነው የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ አላህን በማወቅና እርሱንም በመፍራት ታላቅ ተምሳሌትን ለተከታዮቻቸው ትተውልን አልፈዋል አንድ አማኝ የቱንም ያህል አላህን የሚፈራ ቢሆን የሚያከናውናቸውን የአምልኮ ተግባራት በእርሳቸው መንገድ እስካልፈጸመ ድረስ ፈጽሞ ተቀባይነት የለውም አላህ በቁርዓኑ እንዲህ ይላል መ ፈቨዶ ረሆ ገችሠረ ዶዳ ረ መነ ቃረ ሚመ ኔ ለእናንተ አላህንና የመጨረሻውን ቀን የሚከጅል ለሆነ ሰው አላህንም በብዙ ለሚያወሳ በአላህ መልእክተኛ መልካም መከተል አላችሁሸ አልአሕዛብ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ የሕይወት ፈለግ ለማንኛውም ሙስሊም በቂ ተምሳሌትነት ያለው ለሁሉም የሕይወት ዘርፍ ተስማሚ የሆነም ነው በእርግጥም አርሳቸው ይህችን ዓለም ያሳለፉት እንደ መልካም አባወራ ጥሩ የትዳር አጋርተወዳጅ አባት ተስማሚ ጐረቤት እንከን የማይወጣለት ባልደረባ ቅን መሪ ወዘተ በመሆን ነው ስለዚህም በሁሉም እንቅስቃሴዎቻቸው ያሳዩት የነበረው ፈለጋቸው መለኮታዊ ሞገስ የተቸረው ለመሆኑ በቂ ማስረጃዎችን ማቅረብ ይቻላል አላህ አንዲህ ይላል ። ዕኒጋዕ ኑኔ መልእክተኛው የሰጣችሁን ማንኛውም ነገር ያዙት አልሐሽር ኃ ኳቹ ን ኞነ ኦው በላቸው አላህን የምትወዱ እንደሆናችሁ ተከተሉኝ አላህ ይወዳችልና ኃጢአቶቻችሁንም ለእናንተ ይምራልና አሊዒምራን ሯ መ ይ ለእናንተ አላህንና የመጨረሻውን ቀን የሚከጀል ለሆነ ሰው አላህንም በብዙ ለሚያወሳ በአላህ መልእክተኛ መልካም መከተል አላችሁ አልአሕዛብ ሀኋዴ ድ ኘ ምብ ሬ ሪሯርታሩፌ በጌታህ በራሴ እምላለሁ በመካከላቸው በተከራከሩበት ፍርድ አስከሚያስፈርዱህ ከዚያም ከፈረድከው ነገር በነፍሶቻቸው ውስጥ ጭንቀትን እስከማያገኙ ፍጹም መታዘዝንም እስከሚታዘዙ ድረስ አያምኑም አልኒሳእ እናም የነቢዩን ሰዐወ መንገድ ትተን ወደ ሌሎች ጐዳናዎች የምንገባ ከሆነ ባዝነን ከመቅረት በስተቀር የምናገኘው ፋይዳ አይኖርም ከእርሳቸው ትዕዛዝ ውጪ የሆኑ ነገሮችን መፈጸምም ቢድዓ ፈጠራ ነው የሚሆነው አዲስ የተፈጠረ ነገር ደግሞ ተቀባይነት የለውም ይህን ጉዳይ አጽንኦት ሰጥተው ነቢዩም ሰዐወ እንደሚከተለው በማለት ይናገራሉ ማንም ሰው በዚህ ጉዳያችን ላይ በኢስላም ከእርሱ ያልሆነ አዲስ ነገር ካመጣ አዲሱ ነገር ውድቅ ነው የው ልጅ በታሪኩ ብዙ የድንቁርና ዘመናትን አሳልፏል በእነዚህ ጊዜያት ከተወሰኑ የአላህ ባሪያዎችና ወዳጆች በስተቀር አብዛኛው የሰው ዘር ለዝንባሌውና ለቁሳዊ ፍላጎቱ ሲያድር ኖሯል እነዚያ የአላህ ምርጥ ባሪያዎችና ወዳጆቹ በየተፈጠሩበት ማኀበረሰብ ውስጥ በአርአያነት ሲታዩ የሚከተሉትን ኃላፊነቶች በጫንቃቸው ላይ በማሳረፍ ነው የአላህን አንቀጾች ለሕዝቦቻቸው በማንበብ በሥራ ላይ እንዲውሉ ያደርጋሉ መጽሓፍንና የኃይማኖት ሕግጋትን ለሕዝቡ ያብራራሉ ሌሎች መንፈሳዊ ጥበባትንም ያስተምራሉ ሰዎች የፈጣሪያቸውን ሕግጋት ጠብቀው እንዲጸኑ እስቲቃማህ እንዲኖራቸው ያበረታታሉ ይህንንም ራሳቸው በሥራ በማዋል ያሳያሉ በዚሁ መንገድ ከአባታችን አደም ዐሰ የጀመረው የመለኮታዊ አገዛዝ ሕግ በተሟላና ባማረ ሁኔታ በነቢዩ ሙሐመድ ሰዐወ እስኪደመደም ድረስ ቀጥላሏል እንግዲህ መልካም ነገሮችን አመለ ሷሊህ ለመፈጸም ሁለት ቅድመ ሁኔታዎችን ታሳቢ ማድረግ ተገቢ ነው የአላህን ትፅዛዛት በአክብሮትና በመተናነስ መፈጸም የአላህን ውዴታ በመሻትና ለአርሱ ብሎ ለሰው ልጆችም ሆነ ለሌሎች ፍጡራን ደግነትና ርህራፄን ማሳየት አንዲሁም ቸር መሆን በሌላ አገላለጽ ቅኑን መንገድ መመራት ማለት ሌላ ሳይሆን አላህንና መልእክተኛውን ከልብ መውደድየእነርሱን ትእዛዛት አቅም በፈቀደ መጠን መፈጸምና ክልከላዎችን ግን ሙሉ በሙሉ ማክበር የነቢዩን ሰዐወ የሕይወት ፊለግ መከተል ማለት ነው ከቀናው ጐዳና መዘንበልና ለአላህ ብሎ መልካም ሥራዎችን አለመፈጸም ከፃቅ ማፈንገጥ ነው ይህም ከአላህ ፊት ሥራን ዋጋ ያሳጣል ይህን በመሰለው ቀናነት ውስጣቸው ከተሞላ የኢስላም የበኩር ልጆች መካከል ሁለተኛው ኸሊፋና አልፋሩቅ በመባል የሚታወቁት ኡመር ኢብን አል ኸጣብ ረዐ ይገኙበታል የኸሊፋነቱን መንበር ሲቆናጠጡ እንዲህ ብለው ነበር ለዎች ሆይ። አምር እንዲህ በማለት መልስ ሰጠ አንድ አለት በሆነ ትልቅ ዳገት ላይ ወጥቼ ሰራዊቴን ቁልቁል እመለከት ነበር ጥንካሬአቸውና የቁጥራቸው መብዛት ታላቅ የሆነ እርካታ እንዲሰማኝ አደረገኝ ከዚያም ለራሴ እንዲህ አልኩ ብዩ ሰዐወ በተዋጉባቸው የጦር አውዶች ተገኝቼ ቢሆን ኖሮ በዚያ ቀውጢ ሰአታቸው ይህን በመሰለ ሰራዊቴ እየተረዳሁ ጠላታቸውን ድባቅ አእመታላቸው ነበር ይህን የመሰለ እድሜ ልኬን አብሮኝ የኖረ ምኞት ነበረኝ በዚህ ኢኽላስ ባለው አስተሳሰቤና ፍላጐቴ ምክንያት ኃያሉ አላህ ኃጢአቶቼን ምሮ ለታላቅ ሽልማት አብቅቶኛል ይህ አጋጣሚ ንያን አሳቤን ለአላህ ብሎ ማጥራትና ሥራንም በፍጹም ቅንነት ኢኽላስ መከወን ከአላህ ዘንድ ምን ያህል ታላቅ ደረጃ አንዳለው ያሳያል ይህን አስመልክቶ ነብዩ ሰዐወ የሚከተለውን መናገራቸውን ኡመር ኢብን አል ኸጧብ ረዐ አስተላልፈዋል የአንድ ሰው ተግባር የሚለካው በቁርጠኛ ፍላጉጐቱ በንያው ነው ማንኛውም ሰው እንደ ዛሳቡ ንያው ያገኛል ስደቱ አላህንና ነብዩን ለማስደሰት ዓላማ ከሆነ ስደቱ ወደ አላህና መልእክተኛው ነው የተሰደደው ዓለማዊ ጥቅም ለማግኘት ወይም ሴት ለማግባት ከሆነ ስደቱ ለተሰደደበት ነገር ነው ስለሆነም አንድን ሥራ ከመስራታችን በፊት ዛሳባችንን ንያችንን ቆም ብለን መመርመር አለብን በምንሰራው ሥራ ለማስደሰት ያሰብነው ከአላህ ሌላ የሆነን አካል ከሆነ ያንን ነገር አቁመን ተውበት በማድረግ አላህን የሚያስደስተውን ነገር ብቻ መፈጸም ይኖርብናል ይህም ኢኽላስ ፍጹም ተነሳሽነት ተብሎ ሊገለጽ ይችላል በዚህ ትንታኔ መሠረት ሥራ ልክ እንደ አካል ሲሆን አሳቤ ንያ ደግሞ እንደ ነፍስ ሩህ ሊቀጠር ይችላል ስለሆነም ነፍስ ከታመመች አካልም አብሮ ይታመማል ማለት ነው በዚህ ስሌት መሠረት ሶላት ጾም ሰደቃም ሆነ ማንኛውም የአምልኮት ተግባር በጥሩ እሳቤ ንያ የማይከወን ከሆነ ከአላህ ዘንድ ተቀባይነት የሌለው ብቻ ሳይሆን ሰሪውንም ያስጠይቃል ምክንያቱም በሚፈጽመው አምልኮ አላህን ብቻ ለማስደሰት ከማለም ይልቅ ከእርሱ ውጭ የሆነን አካል ለማስደሰት አልሟልና ይህም ሽርክ ማጋራት የተባለውን ኃጢአት ከመፈጸም ያስፈርጃል ስለሆነም ይህን ዓይነት ድርጊት የሚፈጽሙ ሰዎች የሚተርፋቸው ነገር ድካም ብቻ ነው ማለት ነው በሌላ በኩል አንድ ሰው አላህን ለማስደሰት በመሻት ሌላው ቀርቶ አነስተኛ የሚባሉ ነገሮችን ቢፈጽም እንኳን ምንዳ ማግኘቱ አይቀርም የሰው ልጅ በተወሰነ መልኩም ቢሆን ከሌሎች እንስሳት ጋራ የሚጋራው ደመ ነፍሱን ዝንባሌውን የመከተል አዝማሚይ ይታይበታል። መናፍቅነት ልታይ ልታይ ባይነት አላህን ከማስደሰት ይልቅ መልካም ሥራን በመሥራት ዓለማዊ ጥቅምን መሻት ናቸው ከአላህ ሌላ የሆነ አካል እንዲወድልን እንዲያይልን ወይም እንዲያመሰግነን በመሻት የምንሰራ ከሆነ ይህ ድብቅ የሆነ ማጋራት ሸርክ ነው ከዚህ በታች በሚቀርበው ሐዲስ የምንገነዘበው ቁምነገር የመናፍቅነትና የእዩልኝ ባይነት ሪያእ አስከፊ ውጤት ምን አንደሆነ ነው ከአቡ ሁረይራ በተወራውና ሙስሊም በዘገቡት ሐዲስ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ እንዲህ ብለዋል ሶስት ዓይነት ሰዎች በፍርዱ ቀን ከሰው ሁሉ በፊት አላህ የእነርሱን ጉዳይ ይፈርዳል የመጀመሪያው ሰማእት ሸሂድ በመሆን የተገደለ ሲሆን አላህ ፊት እንዲቆም ይደረግና አላህ የዋለለትን ፀጋ አንድ በአንድ ይቆጥርለታል እርሱም እነዚያን ፀጋዎች ሁሉ ማጣጣሙን ይናዘዛል ከዚያም አላህ እንዲህ ይለዋል የዋልኩልህን ፀጋዎች ለመክፈል ለእኔ ብለህ ምን አድርገዛፃል። ይህን ጉዳይ አስመልክተው የአላህ መልአክተኛ ሰዐወ እንዲህ ብለዋል አላህ የባሪያውን ደረጃ ከፍ ለማድረግ ጥንቱኑ ይወስንለታል ሆኖም ግን ባሪያው በመልካም ሥራዎቹ እዚያ ደረጃ መድረስ አልቻለም በዚህ ጊዜ አላህ የተወሰኑ መከራዎችንና ፈተናዎችን ይልክበታል ከዚያም በማስከተል እነዚያን ፈተናዎቹን የሚሸከምበት ትዕግስት ያጎናጽፈዋል ያንን የወሰነለትን ደረጃም ያገኛል ሙስነድ አቡ ያዕላሶሂህ ኢብን ሂባን ነቢዩ ሙሣ ዐሰ ከአላህ ጋር ለመነጋገር በሲናይ ምድረበዳ ወደ አንድ ተራራ እየወጡ ሳሉ አንድ ሰው ያጋጥማቸዋል ሰውየውም ሙሳን ዐሰ እንዲህ አላቸው አንተ ከአላህ ጋር የምትነጋገረው ከሊሙሏህ ሆይ። እርሷ ፈተናይቱ ያንተ ፈተና እንጂ ሌላ አይደለችም በአርሷ የምትሻውን ታሳስታለህ የምትሻውንም ታቀናለህ አንተ ረዳታችን ነህና ለእኛ ምህረት አድርግልን አዘንልንም አንተም ከመሐሪዎች ሁሉ በላጭ ነህ አልአዕራፍ ከዚህ አገላለጽ የምናስተውለው ነገር ሌላው ቀርቶ ነቢያትም ቢሆኑ እንኳን ከፈተና የማያመልጡና ልቦቻቸውም እጅግ አስፈሪ የሆኑ መከራዎችን እንደሚጋፈጡ ነው ከዚህ ፈተና መጨረሻ ላይም እነርሱ ምንጊዜም በተስፋና በፍርፃት መካከል ሆነው ሕዝባቸውን መምራታቸውን እንደሚቀጥሉ እአንገነዘባለን ሁላችንም ብንሆን በፀጋ ላይም ሆንን በመከራችን ሰዓት አላህን አእየፈራንና አዝነቱንም ተስፋ እያደረግን መጓዝ ያለብን መሆኑ ግልጽ ነው ምዕራፍ ሰባት ግድየለሽነት አንድ ሰው በምድረበዳ እየተጓዘ እያለ ሳያስበው ከአንድ አደገኛ አውሬ ጋር ይገናኛል ይህ ሰው ምንም ያክል በፍጥነት ቢሮጥ ከዚህ አይምሬ የሆነ የዱር አውሬ ሊያመልጥ አንደማይችል አመነ ሆኖም ግን ተስፋ ቆርጦ ሞትን ከመጠባበቅ በደመነፍስ ከአቅራቢያው ከሚገኝ ጉድጓድ ውስጥ ዘሎ ገባ ወደ ጉድጓዱ ውስጥ እየገባ አያለ በጉድጓዱ ግድግዳዎች ላይ የበቀሉ ቁጥቋጦዎችን በማግኘቱ የሞት ሞቱን ሙጭጭ አድርጐ በመያዝ ወደ አዘቅት ከመውረድ ይድናል ሆኖም ግን በዚያው ቅጽበት ቁልቁል ሲመለከት አጅግ መርዛማ የሆኑ አባቦችና ዘንዶዎችን ሊበሉት ሲርመሰመሱ ያያል ሽቅብ ሲመለከት ደግሞ ነጭና ጥቁር መልክ ያላቸው አይጦች በእጁ ጨምድዶ የያዛቸውን ቁጥቋጦዎች ሥራቸውን በጥርሳቸው እአየገዘገዙ እንደሆነ አስተዋለ በዚህ ጊዜ ፍርሃት አንዘፍዝፎ ከሞላ ጐደል ህሊናውን ሊያስተው ቀረበ በዚህ ሁኔታ ውስጥ እያለ ጥቂት ጊዜ እንደቆየ በጉድጓዱ አንድ ጥግ ላይ ማር የሞላበት ቀፎ አስተዋለ ከዚያም ለራሱ እንዲህ አለ እንደምንም ብዬ ከዚህ ማር መቅመስ አለብኝ ምክንያቱም ሌላ ጊዜ ይህን የመሠለ እድል ላላገኝ አችላለሁና ሰውየው ይህን ካለ በኋላ ምንም እንኳን ያን በመሰለ አደጋና አጣብቂኝ ውስጥ ቢሆንም ያጋጠመውን ነገር ለጊዜው በመርሳት ማሩን በመላሱ ላይ ብቻ ተማረከ የማሩ ጥፍጥና ያጋጠመውን ታላቅ አደጋና ያንዣበበበትን የሞት ጥላ እንዳይመለከት አይኑን ያወረው ሲሆን ሕሊናውንም ጋርዶታል አናም ሰውየው እንደምንም ብሉ ከጉድጓዱ በመውጣት ነፍሱን በማትረፍ ፋንታ ማሩን መላሱን የቀጠለ ሲሆን በተመሳሳይ ሰዓት እነዚያ አይጦች ቁጥቋጦዎችን ቆርጠው በመጨረሳቸው ወደ ጉድጓዱ ወድቆ አርፏል በዚህ ተምሳሌታዊ ትረካ ጉድጓዱ የሚወክለው የዚህችን ዓለም ኑሮና በውስጧ የያዘቻቸውን መከራዎች ሲሆን አባቦቹና ዘንዶዎቹ ደግሞ መጥፎ ባሕሪያቶችን ሥራዎችን ነው ማሩ የሚወክለው ለጊዜያዊና ጠፊ ጥቅም መስገብገበን ነው ነጭና ጥቁር የተባሉት ሁለት አይጦች በሰው ልጅ ሕይወት ላይ የሚያልፉ የሆኑት ቀንና ሌሊት ናቸው ተጓጉዞ ሰው ደግሞ ግዴለሽ ጋፊል የሆነና ለመጪው ዓለም የፍርዱ ቀን ምንም ዝግጅት የማያደርግ ሰው ነው አይጦቹ የቁጥቋጦዎቹን ሥሮች በሹል ጥርሳቸው ቀረጣጥፈው ሲጨርሷቸው ቁጥቋጦዎቹ ስለተነቀሉ ሰውየውን ወደ ጉድጓዱ አዘቅት ከመውረድ የሚጠብቀው ነገር ሊኖር አይችልም እናም ወድቆ የእባቦችና ዘንዶዎች ሲሳይ ሆነ በዚህ ትረካ በግርድፉ ለማሳየት የተሞከረው የሰው ልጅ ወደዚህች ዓለም የተላከው ለታላቅ ዓላማ ቢሆንም እርሱ ግን ኃላፊ በሆነው ሥጋዊ ፍላጎቱ የሚሸነፍ መሆኑን ነው አንግዲህ የሰው ልጅ ሲባል ከመጪው ዓለም ታላላቅ አደጋዎች ለመዳን ከፈለገ ከመጥፎ ምግባራት ራሱን ማንጻት ጊዜውንም በአግባቡ መጠቀም ይኖርበታል በምድር ገጽ ላይ የሚገኙ ሁሉም ፍጥረታት በተፈጥሮ የተነደፈላቸውን የአኗኗር ዘይቤ ተከትለው በመጓዝ ብቻ ደስታን የሚያጋኙ ይመስላሉ የሰው ልጅ ግን የእነዚያ ሁሉ ፍጡራን የበላይ ቢሆንም የቀልብ ደስታ የሚያገኘው የአላህን ሕግ አክብሮ መጓዝ ሲችል ነው ከአላህ ህግ ሸሪዓ ውጭ ያለ ሕይወት የድንቁርና ሂሊያ ሕይወት ሲሆን ይህም የስቃይና የመከራ ሕይወት ነው ይህን የመሰለ የሕይወት ዘይቤን የሚከተል ሰውም ግድየለሽ ጋፊል ይባላል የሰው ልጅ የተፈጠረበትን ዓላማ አሁን የሚገኝበትን ሁኔታ በሕይወት የመገኘቱን ምስጢርና ከዚህ ሁሉ ጀርባ ያለውን ጥበብ አለማስተዋሉ ከንቱነት ነው በእርግጥ አንድ ብልህ ወይም አስተዋይ ሰው የሰው ልጅ ካልነበረበት ኢምንት ከሆነ ነገር ወደዚህች ዓለም የመምጣቱንና ከተወሰነ ፈተና በኋላም የመሞቱን ጥበብ ለማወቅ አለመፈለጉ ያስደንቃል ሰው ሆኖ የመፈጠርን እውነተኛ ዓላማ አንዲሁም የሕይወትንና የሞትን ምንነት ለማወቅ የመጀመሪያው እርምጃ ግዴለሽነትን ማስወገድ ነው ይህንንም ለማድረግ የሚቻለው እውነተኛ በሆነ ምክንያታዊነትና በመንፈሳዊነት ማስተንተን በጉጐለበተ ልቦና ቀልብ ነው ተፈጥሯዊ የሆኑ እንደ ቸልተኝነት ስግብግብነት ኩራት የተጋነነ ተስፋ ቅናት አባካኝነትና ንዴት የመሳሰሉት የሰው ልጅ ዝንባሌዎች የግዴለሽነት ገፍላ መገለጫዎች ናቸው እነዚህ ባህሪያት የሰውን ልጅ ጠፍንገው በመያዝ በራሳቸው እሽክርክሪት ውስጥ የሚያዞሩት ከሆነ ታላቅ ጥፋት ላይ ወድቋል ማለት ነው የሰው ልጅ በእነዚህ ባሕሪያትና በነፍስያው አንድ ጊዜ ከተቀየደ የሐቅን መንገድ ለመያዝ ከቶም አይቻለውም ከዚያ በኋላ ሕሊናው የጨለመ ክብሩ የተዋረደና ፈጣሪውንም የሚስተባብል ሆኖ ያርፈዋል ይህን በመሰለ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ሰዎች አላህ የሚጠብቃቸውን አሣር በሚከተሉት የቁርአን አንቀጾች ይገልጻል ኢ ፊ ና ኅሸየ ጄ » ፕጭሠ መዕ ። አልጃሲያህ በአንድ ሰው ልብ ውስጥ የሞራል ይዞታ ሲዳከምና ሲያሽቆለቁል መንፈሳዊ ለሆኑ ነገሮች የሚሰጠው ክብርና ግንዛቤም የዚያኑ ያክል ይዳከማል እንዲህ አይነቱ ሰው ደግሞ በአምልኮት ላይ ጽናት ኢስቲቃማህ አይኖረውም በኃጢአት አረንቋ ውስጥ የተዘፈቀ ሰው በዚያው ሁፄታው እስከቀጠለ ድረስ የሕሊናው ዓይን ስለሚታወር ያለበትን ሁኔታ አይገነዘብም ግዴለሽ የሆኑና በነፍስያቸው ጣጣ የተዋጡ ሰዎች በኃጢአታቸው ምክንያት የሚደርስባቸውን አፍራሽ ሁኔታ እንዳያስተውሉ አይናቸው የሚታወር ሲሆን ጆሮአቸውም ይደነቁራል ጣቱ የቆሰለ ሰው ምንም ነገር ሳይሰማውና ሳይጸየፍ ምግቡን እየቆረሰ ሊመገብ ቢችል እንኳ ከአርሱ ጋር አብረው በማአድ የታደሙ ሰዎች የእርሱን ቁስል እያዩ ምግቡ ሊያስጠላቸው ይችላል በተመሳሳይ ሁኔታ ሕይወታቸውን በዘፈቀደ የሚመሩ ሰዎች እንዳሉ አይሰማቸውም ለእነርሱ ስሜትና መረን ለለቀቀ ራስ ወዳድነታቸው አእስከተስማማ ድረስ ሌላው የፈለገውን ቢሆን አይገዳቸውም አነርሱ በአርግጥም አንድ የጦር ሰው ሰውነቱን በጡሩሩ የብረት ልብሱ ውስጥ እንደሚደብቀው ሁሉ በኃጢአት ማቅ ተጀቡነው ያሻቸውን ማድረግ ያስደስታቸዋል አነዚህ ሰዎች ለሃቅና መለኮታዊ ለሆኑ ግሳጹዎች ጆሮ ዳባ ልበስ ያሉ አውሮች ደንቆሮዎችና ዲዳዎች ናቸው አቡ ያዕላ ሸዳድ ኢብን አውስ ረዐ ባወሩትና ቲርሚዚ በዘገቡት ሐዲስ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ እንዲህ ብለዋል አዋቂና ብልህ ሰው ማለት ሥጋዊ ፍላጐቱንና ስሜታዊ ዝንባሌውን ተቆጣጥሮ ከሞት በኋላ ላለው ሕይወቱ የሰራ ሰው ነው ሞኝ ተላላና ደካማ ሰው ማለት ደግሞ ራሱን ወደ ተከለከሉና አጥፊ ወደሆኑ እኩይ ምግባራት በምትመራው ነፍሱ ስሜታዊ ዝንባሌ ቁጥጥር ሥር አውሎ የዝንባሌው ተከታይ በመሆን ምህረትና ፀጋውን ያላንዳች ጥረት በባዶ ምኞት ከአላህ ምህረት የሚጠብቅ ሰው ነው ምዕራፍ ስምንት ወደ አላህ መቃረብ አንድ የአላህ ባሪያ ከኃጢአት ርቆ የእውነትን መንገድ ሲይዝ አላህ ይበልጥ ወደ እርሱ እየቀረበ እንደሚመጣ ይታወቃል ይህም በተከታዩ ሐዲሰል ቁድስ ይበልጥ ተገልዷል ከአነስ ረዐ በተወራው መሠረት ነብዩ ሰዐወ አላህ እንዲህ ብሏል አሉ አንድ አገልጋዬ ባሪያዩ አንድ ስንዝር ወደእኔ ሲቀርብ እኔ አንድ ክንድ ወደርሱ አቀርባለሁ አንድ ክንድ ሲቀርበኝም አንድ አርምጃ አቀርበዋለሁ እየተራመደ ወደኔ ሲመጣም እኔ እየሮጥኩ ወደርሱ አመጣለሁ ይህም በመሆኑ ወደ አላህ ለመቃረብ የሚፈልግ ሰው የሚከተሉትን ሁኔታዎች በሚገባ ማጤንና መተግበር ይጠበቅበታል ተውባ ማድረግ የኃጢአትን ጥንስስ በልብ ላይ ከሚጥሉ ነገሮች መካከል የድንቁርና ጃሂሊያ ተግባራት የወሲብ ፍላጐት ኩራት ንዴት ብስጭት ጥለቻ ከንቱ ምኞት ቅናት ጋጠወጥነትና አባካኝነት ጥቂቶቹ ናቸው እነዚህና መሰል ባህሪያት አንድ ሰው ከፈጣሪው ጋር የሚኖረውን ዝምድና መቃረብ አጅጉን የሚጐዱና ከአርሱም የሚያርቁ ናቸው አንድ ሰው የራሱን አቋም በየጊዜው የሚመረምርና እርምጃውንም ከፈጣሪው ፍላጐት ጋር እያስተካከለ የሚጓዝ ካልሆነ በሰራቸው መጥፎ ድርጊቶች ሳይረበሽና መንፈሱም ሳይታወክ አይቀርም ፈጣሪው በውስጡ ያስቀመጠው ሕሊናው ድምጹን እያሰማ ልቡን ያውከዋል በዚህ ጊዜ ዝናብ እንዳረገዘ ዳመና ዛሣዘንና ፀፀት የከበደው መንፈሱ እዝነ ልቦናውን በመቀስቀስ እንባው ከዓይኑ እንዲንከባለልና ወደፈጣሪውም የእርቅ መንገድን እንዲፈልግ ያደርገዋል ይህ በሃዘንና በፀፀት ተነሳስቶ በአንባ እየታጀበ የሚቀርብ መቃተት ተውባ ንስፃ ተብሉ ይጠራል ሞት ሳይወስደው በፊት በፈቃዱ ወደ ፈጣሪው የሚመለስበትና የኃጢአት ሥርየት የሚጠይቅበት ሂደት ነው ተውባ በሌላ አገላለጽ ተውባ ንስዛ ማለት በሰውና በፈጣሪው መካከል ደንቃራ በመሆን ግንኙነታቸውን ያውክ የነበረውን የኃጢአት ጋሬጣ በፀፀት ማስወገድ ማጽዳት ነው የሰው ልጅ ወደ ፈጣሪው መቃረቢያ ከሚያደርጋቸው መንገዶች ተውባ የመጀመሪያው የሆነበት ምክንያት ኃጢአት የልብን ኃይልና ኃጢአትን የመቃወም ብቃቷን እንዲሁም የህሊናን ድምጽ ስለሚያደክም ነው ይህንም ሁኔታ ጥላሸት በተቀባ መስታወት መልክን ከመመልከት ጋር ማመሳሰል ይቻላል በዚያ ቆሻሻ መስተዋት ትክክለኛውን ገጽታችንን እናይ ዘንድ ልናጸዳውና ጭጋጉን ልናስወግድለት ግድ ነው በተመሳሳይ ሁኔታ ከኃጢአት በመወገድ ተውባ አድርጐ ወደ አላህ መመለስ ልብን የጋረዳትን ጽልመት የመወልወል ያህል ይቆጠራል አላህ እንዲህ ይላል ሠ ረረ ነነለ ። ነብዩ ኢብራሂም ዐሰ ወደ እሳት ሲወረወሩ ያሉት ቃል ሲሆን ነብዩ ሙሐመድም ሰዐወ ሰዎች ጦር አከማችተውላችኋልና ፍሯቸው ሲባሉ ሁኔታው ይበልጥ ኢማን አምነት ጨምሮላቸው ይህንኑ ቃል ሐስቡነሏሁ ወኒዕመል ወኪል ብለዋል በማለት ኢብን አባስ ረዐ አስተላልፈዋል በሌላ አቡ ሁረይራ ረዐ ባስተላለፉትና ሙስሊም በዘገቡት ሌላ ሐዲስ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ እንደሚከተለው ብለዋል ልቦቻቸው እንደ አሞራ ልብ የሆኑ እንደ አእዋፍ ልቦቻቸው የረቀቁ ወይም ልቦቻቸው በአላህ ፍርሃት የለሰለሱና በማንኛውም ጉዳያቸው በአላህ ላይ ብቻ ተወኩል የሚያደርጉ ብዙ ሕዝቦች ጀነት ይገባሉ ብለዋል የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ እንዲህም ብለዋል በአላህ እውነተኛና ተገቢ የሆነ ተወኩልን መመካትን የምትመኩ ብትሆኑ ኖሮ ማለዳ ባዶ ሆዱን ወጥቶ ማታ ሲመለስ ሆዱን ሞልቶና ጠግቦ ለሚመለሰው አሞራ ሲሣይ እንደሰጠ ሁሉ ለእናንተም በሰጣችሁ ነበር ሐዲሱን ኡመር ረዐ ያስተላለፉት ሲሆን ቲርሚዚ ሀሰን ነው ብለዋል ራራ ዚክር አላህን ማስታወስ ኃያሉ አላህ ዚክርን አርሱን ማስታወስን አስመልክቶ እንደሚከተለው ይላል ቄህሯ ሹ አስታውሱኝ አስታውሳችኋለሁና አመስግኑኝም አትካዱኝም አልብቀራህ ራፊ ራ ቹ ዥ ፌ ኦነ። አላህን በማውሳት ልቦች ይረካሉ አር ረዕድ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ የሚከተለውን መናገራቸውን አቡ ሁረይራ አስተላልፈዋል አንድን አማኝ ካለበት ዓለማዊ ጭንቀት የገላገለ ሰው አላህ ከፍርዱ ቀን ጭንቅ ይገላግለዋል የተቸገረን ሰው የረዳ አላህ በዚህም ሆነ በተከታዩ ዓለም ችግሩን ያቃልልለታል የአንድን ሙስሊም ነውር የሸፈነ አላህ በቅርቢቱ ሕይወት አዱንያም በአኹራም የአርሱን ነውር ይሸፍንለታል እውቀትን ለመፈለግ ጉዞ የጀመረ አላህ ወደ ጀነት የሚወስደውን መንገድ ያገራለታል ሰዎች ከአላህ ቤቶች በአንዱ ተሰብስበው የአላህን መጽሐፍ በሚያነቡበት በጋራ ጥናት በሚያደርጉበት ወቅት በእነርሱ ላይ እርጋታ ይሰፍናል የአላህ እዝነትም ይከብባቸዋል መላእክትም ያጅቧቸዋል አላህም ለእርሱ ቅርብ በሆኑ ክፍሎች መላእክት ዘንድ ያወሳቸዋል ሥራው ወደ ኋላ የሚጐትተው ዘሩ ወደፊት አያስቀድመውም ሙስሊም የዘገቡት ሐዲስ ሶብር ትዕግስት ሶብር ትዕግስት ብለን የምንጠራው አንድ ሰው ለአላህ ፈቃድና ውሳኔ ራሱን የሚያስገዛበትን አጠቃላይ ሁኔታ ነው ይህም ይበልጥ የሚስተዋለው ሰውየውን በሚያጋጥሙት የተለያዩና የማያስደስቱ አለፍ ሲልም የሚፈታተኑ ክስተቶች ጊዜ ነው አንድ ሰው ሶብር ትዕግስት አደረገ የሚባለው አላህ ጥንቱኑ በቀደር የወሰናቸው ነገሮች በአርሱ ላይ ሲከሰቱ ውስጣዊውም ሆነ ውጫዊው ባሕሪው ሳይቀየር አንዳመጣጣቸው ማስተናገድ ሲችልና በሁሉም ሁኔታ አላህን ሲያመሰግን ነው። አላህ ነገሮችን በልክ እንደሚያወርድና በይበልጥም ደግሞ ሲሳይን ሲለግስ የባሮቹን ሁኔታ ባህሪ የገንዘብ አጠቃቀም ብልዛትን ወዘተ ታሳቢ አድርጐ መሆኑን እንዲህ በማለት ይገልጻል ኣራ ለይ ር የ ባሬ አላህ ለባሮቹ ሁሉ ሲሳይን በዘረጋ ኖሮ በምድር ውስጥ ሁሉም ወሰን ባለፉ ነበር ግን የሚሻውን በልክ ያወርዳል እርሱ በባሮቹ ውስጥ አዋቂ ተመልካች ነውና አሹሹራ የሰው ልጅ ሪዝቁ ተወስኖ የተቀመጠው ከመፈጠሩ በፊት እንደመሆኑ ለአላህ ፈቃድ ራሱን በማስገዛት በቀደር የማመንን ጣፋጭ ለዛ ሊያጣጥም ይቸላል የሚከተለው አባባል በሐዲስ አልቁድስ ተጠቅሶ እናገኘዋለን አላህ የሰዎችን ሪዝቅ ሲሳይ የማያከፋፍሉ ለሆነ መላእክት እንዲህ በማለት ያዛቸዋል በመጪው ዓለም ጉዳይ ላይ ብቻ ተመስጦ ለምታገኙት ባሪያዬ የሰማይንና የምድርን በረከቶች ስጡት ባሪያዬ ሲሳዩን ለማግኘት ቀናውን ጉዳና እየተከተለ ካገኛችሁት ለአርሱ መልካም በመሆን መንገዱ እንዲገራለት አድርጉ ነዋዲር አልኡሱል ይህ ሐዲስ በግልጽ አንደሚያሳየው አንድ የአላህ ባሪያ አላህን በመግገዛት ላይ ትኩረቱን ሲያደርግ የእርሱን ትአዛዛት ሲያከበርና የእርሱን ውዴታ በመሻት ሁለንተፃውን ሲያስገዛና ሐቀኛ የአላህ ወዳጅ በመሆን ተቅዋ ያለው ይሆናል ለእንዲህ አይነቱ ሰው ደግሞ ከሰማይም ሆነ ከምድር የአላህ በረከቶች ይከፈቱለታል አላህ በቁርአን እንዲህ ይላል ሁ ን ርዎ ሠን አ ቓበሯሙመጄ አላህንም የሚፈራ ሰው ለእርሱ መውጫን ያደርግለታል ከማያስበውም በኩል ሲሳይን ይሰጠዋል በአላህም ላይ የሚጠጋ ሰው እርሱ በቂው ነው አላህ ፈቃዱን አድራሽ ነው አጥጦላቅ ኡመር ረዐ ባወሩትና ቲርሜዚ የ ሐሰን ደረጃ በሰጡት ሐዲስ የአላህ መልእክተኛ ሰወ አንደሚከተለው ብለዋል እውነተኛና ተገቢው የሆነ ተወኩል መመካት በአላህ ላይ ቢኖራችሁ ማለዳ ባዶ ሆዱን ወጥቶ ማታ ሲመለስ ሆዱን ሞልቶና ጠግቦ ለሚመለሰው አሞራ ሲሣይ እንደሰጠ ሁሉ ለእናንተም በሰጣችሁ ነበር በፍጥረተ ዓለሙ ውስጥ ልክ እንደ ጉንዳን ለክረምት ወራት ምግባቸውን የሚያስቀምጡ ነፍሳት ጥቂት ናቸው አብዛኛዎቹ ለከፋ የክረምት ወቅት እንኳ ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ምግባቸውን አያከማቹም አንዲያም ሆኖ በህልውና የሚያቆያቸውን ጥንካሬ በማግኘት ለፀደይ ወራት መዝለቅ አይሳናቸውም ብቃትና አስተማማኝነት ባለው መለኮታዊ አገዛዝ ሥር ፍጡራን እንዴት የእለት ጉርሳቸውን አያገኙም ተብሎ ይታሰባል። ይሁን እንጂ ስንፍና ስግብግብነት ቅናት ልጆች እንዳይወለዱ መፈለግ ወዘተለሪዝቃችን ሲሳያችንነ መጥበብ ተጠያቂ የሆኑ ጋሬጣዎች ናቸው አንግዲህ ኢስላም የሚያስተምረን እያንዳንዱ ሰው የአለት ጉርስ ሪዝቅ አስቀድሞ የተወሰነ ሲሆን አይጨምርም አይቀንስም የሰው ልጅ ከተፈጠረባት ቅጽበት ጀምሮ የሚተነፍሳት አየርና የሚጐርሳት እያንዳንዲ ጉርሻ በልክ ተወስና የተቀመጠች ናት ይሁን እንጂ ይህንን የአለት ጉርስን ለማግኘት ተግቶ መንቀሳቀስ በአማኞች ላይ ግዴታ የሆነ ተግባር ነው ስለሆነም አላህን መታዘዝና ለሪዝቃችን ሲሳያችን መንቀሳቀስ ግዴታችን ነው ማለት ነው ይህ ማለት በሌላ አባባል በቀደር የተጻፈልን ሪዝቃችንና እርሱን ለማግኘት የምናደርገው ጥረት በጽኑ የተሳሰሩ ናቸው ማለት ነው አንድ የቱርኮች አባባል አለ በቂ የሆነ ጥረት ሳታደርግ በዛሃሰት በቀደር አታመካኝ ይላል ኃያሉ አላህ ነጻ ፈቃድ ሰጥቶናል የሥራ ፈጠራ ኃላፊነትን መሸከም የመምረጥ ነጻነትና ማስተዋልን የመሳሰሉ ብቃቶችን አላብሶናል እነዚህን ነገሮች ችላ ማለትና ለድህነት እንዲሁም ለተረጂነት መዳረግ በእውነቱ በአላህ ላይ እንደማመጽ ነው የሚቆጠረው ራሳችንን ከአደጋ መጠበቅ በተፈጥሮ የምንወርሰው ነገር ነው ለምሳሌ ስንታመም ወደ ሃኪም ዘንድ መሄድ አደገኛ የሆነ እሳት ወይም ርእደ መሬት ሲያጋጥመን ከዚያ ሥፍራ መሸሽ ከዚህ ተፈጥሮአዊ ባህሪያችን የወረስነው ነው በሌላ በኩል ሪዝቃችንን ወዲያና ወዲህ ተሯሩጠን መፈለግ ከአደጋ ሚጠብቀን መለኮታዊ ትእዛዝ ነው ይህን ማድረጋችን ከቶም በቀደር ከማመናችን ጋር ፈጽሞ የሚጋጭ አይደለም ከአስባብ ጋር የመጋጨትን ሕግ መጣስ በራሱ በአላህ ላይ እንደማመጽ የሚቆጠር ሲሆን ይህም ታላቅ የሆነ ኃጢአት ነው አላህ በቁርአኑ እንዲህ ይላል ፓ መጻ ጩጃመጋጩን ለሰውም ሁሉ የሰራው እንጂ ሌላ የለውም አንነጅም ታላቁ መልእክተኛ ሙሐመድ ኢብን አብዱላህም ሰዐወ እንዲህ ብለዋል አንድ ሰው ከሰዎች ከመለመን ገመድ ይዞ ወደ ጫካ በመሄድ በእንጨት ሰብስቦ እየሸጠ ቢተዳደር ይሻለዋል ሰዎች የሚፈልገውን ቢሰጡትም ቢነፍጉትም ቡኻሪ የዘገቡት ኢብን አል ፊራሲ እንዳስተላለፉት አንድ እለት አባታቸው ነብዩን ሰዐወ እንዲህ በማለት ጠየቋቸው የአላህ መልክተኛ ሆይ። ይሁን እንጂ መጠየቅህ ግድ ከሆነ ምእመናንን ጠይቅ ነሳኢ አቡ ዳውድና ኢብን ማጃህ ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ ኃያሉ አላህ አንዱን ፍጡር ለሌላው ጉርስ የማግኛ ሰበብ አድርጐ ነው የፈጠረው ይህም በመሆኑ ድሆችን መንከባከብ የእነርሱን ፍላጐት ማሟላትና አላህ በለገሰን ነገር የእነርሱን ችግር መቅረፍ እንደ ታላቅ መልካም ሥራና ጽድቅ ይቆጠርልናል ጂብሪል ዐሰ የሚከተለውን መናገሩ ተወስቷል እኔ ከዚህ ዓለም ሕዝብ መካከል ብሆን ኖሮ ሶስት ነገሮችን ከሁሉም በላይ እወድ ነበር መንገድ የጠፋቸው ሰዎችን ማመላከት አላህን በድህነት ላይ ሆኖ የሚያመልክን ሰው እንዲሁም በድህነት ላይ ሆነው ብዙ ልጆችን የሚያሳድጉ ሰዎችን መርዳት የተፈቀዱ ፃላል ምግቦች በአላህ የምናምን ሰዎች ሁሉ የትኩረት ማዕከል መሆን ያለበት ሌላው ነጥብ የምናገኘው ሲሳይ ምግብ የተፈቀደ ፃላል ከሆነ ምንጭ የተገኘ ከመሆኑ ላይ ነው አንድን ሰው ቀናውን መንገድ ተከትሎ እንዲጓዝ ትልቅ አትስተዋጽኦ የሚያደርግለት የሚመገበው ሲሳይ ዛላል መሆኑ ነው ፃላል የተፈቀደንን ምግብ መመገብ ለሕይወት ብርዛን ለልብ ደስታን ለአምልኮት ኢባዳ ለዛን ያላብሳል የተስተካከለችና አላህን የምትፈራ ቀልብ ልብ እንድትኖረንም ወሳኝ ነው በሌላ በኩል ደግሞ ፃራም የሆነ ምግብ ሕይወትን የሚያበላሽ መርዝ ሲሆን ለቀልብም ጨለማን ያላብሳል በዚህ ዓለም ላይ የሚታየው የዘቀጠ ስርዓትና በመጪውም ዓለም የሚያጋጥመው ውርደት የዚሁ ህገወጥ ፃራም የሆነ ሲሳይ አስፈሪ ውጤት እንጂ ሌላ አይደለም ሃላል የተፈቀደ ገቢና ምግብ ከአላህ ዘንድ ለመቃረብ ሰበብ የሚሆኑ ሲሆን በተቃራኒ ፃራም ህገወጥ ከሆነ ገቢ የተገኘ ገንዘብና ምግብ ለታላቅ ፀፀትና መከራ የሚዳርግ የእሳት ጉርስ ነው የአንድ ሰው ቀልብ በአላህ ፈንታ በገንዘብና በልጆች ፍቅር ሲሞላ መጨረሻው ዛዘንና ተስፋ መቁረጥ ነው አላህ በቁርአን እንዲህ ይላል ፌሬቨ ኦኗዌር መ ሂጄጌ እናንተ ሰዎች ሆይ። ልጄ ግን የዚህን አንቀጽ ትርጉም በሚገባ ተረድቶት ነበር በአርግጥ ቁርአን ለሚያነበው ሰው እንደታላቅ ውቂያኖስ ውስጡን መርምሮ መጨረስ የማይቻል የአላህ አደራ ነው ስለሆነም ቁርአንን ማንበብ ከኢባዳ ዓይነቶች ሁሉ ምርጡ ነውና ሁላችንም በሶላታችንም ላይ ይሁን በሌላ ጊዜ በተመስጦ ማንበብ ይኖርብናል ቁርአንን ስናነብ እንደ ቀላል መቁጠር የለብንም ትኩረት ሰጥቶ ማንበብ ያስፈልጋል ጳሎ ወይም በርሱ ላይ ጨምር ቁርአንንም በዝግታ ማንበብን አንብብ አልሙዘማል ቁርአን በሚቀራበት ጊዜ በጽሞና እንድናዳምጥ አላህ እንዲህ በማለት ያዘናል ዝረ ህይ ጻ ፕሂ ቁርክንም በተነበበ ጊዜ እርሱን አዳምጡ ፀጥም በሉ ይታዘንላችቷልና አልአዕራፍዐ ቁርአን ሲነበብ ፀጥ ብሎ ማዳመጥ በውስጡ የያዘውን መልእክት ለመገንዘብ ያግዛል መገንዘቡ ደግሞ የእውቀት ባለቤት ያደርጋል እውቀት ያለውን ሰው ደግሞ አላህ ያዝንለታል የአላህ መልእክተኛም ሰዐወ በዚህ ረገድ ታላቅ የሆነ ተምሳሌትን ትተውልናል አብደላህ ኢብን መስዑድ ረዐ ቁርአን አንዲቀራላቸው ይጠይቁትና ከዚያም በታላቅ አክብሮትና መንፈሳዊ ጉጉት ሲያዳምጡ ከቆዩ በኋላ አይኖቻቸው በእንባ ይሞላሉ በተመሳሳይ ሁኔታ ልጆቻቸው ቁርዓንን በሚያምር ድምጽና የአነባበብ ስልት ሲያነቡላቸው የሚያዳምጡ ወላጆች የታላቅ አደብ ባለቤቶች ናቸው ወላጆችን መውደድና ማክበር ጠንካራ የሆነ ተፈጥሮአዊ ዝንባሌ መሆኑ ይታወቃል ይሁን እንጂ ከዚህ የበለጠ ጠንካራ የሆነው ፍቅር ወላጆቹ ለልጆቻቸው ያላቸው ፍቅር ነው ይህ ወላጃዊ ዝምድና ሁሉንም የፍቅር ዓይነቶች የመቆጣጠርና የበላይ የመሆን ኃይል አለው እንደዚያም ቢሆን ቁርዓን የሚያስጠነቅቀን ለልጆቻችን ልናደርግላቸው የሚገባንን ወላጃዊ ግዴታ ችላ እንዳንል ነው ወላጆች ልጆቻቸውን ኢስላማዊ ትምህርቶችን በማስተማር የሚኮተኩቷቸው ከሆነ ከአላህ የሆነ በረከት ያገኛሉ ያን ሳያደርጉ ቀርተው አንዲሁ እንዲያድጉ ከለቀቋቸው ግን ለእነርሱም ሆነ ለማኀበረሰቡ የመከራ ምንጭ ይሆናሉ ወላጆች ልጆቻቸውን በቁርአን አስተምህሮት በሚገባ ካነዷቸው የሚገጥማቸውን ሽልማት ነብዩ ሰዐወ ሲናገሩ እንዲህ ብለዋል ቁርክንን በሚገባ የሚያነቡ ልጆች ያሏቸው ወላጆች በፍርዱ ቀን የኑር ብርፃን አክሊል ይደፋሉ የኑር ካባም ይደርባሉ አቡ ዳውድ አህመድ አልዛኪም ብዙ ወላጆች እንዲህ ዓይነት ልጆች አንዲኖራቸው ይመኛሉ ይህም የተለመደና በእያንዳንዱ ወላጅ ተፈጥሮ ውስጥ ያለ ነገር ነው ሆኖም ግን ወላጆች ይህን ነገር ለማድረግ ሲነሱ ሊያስከፍል የሚችለውን መስዋእትነትም ጠንቅቀው መገንዘብ ይኖረባቸዋል ይህን ማድረጋቸው የአላህን ፈቃድ መፈጸማቸው እንደሆነና ለዚህም ታላቅ ጥረታቸው ተገቢውን ምንዳ ከዓለማት ጌታ አላህ ያገኛሉ አንድ ሰው በያዘው ነገር ላይ ከልቡ ከጣረ ቤተሰቡን ለመቀለብ የሚያደርገው ልፋት እንኳ ምንዳ የሚያስገኝለት መሆኑ ታላቅ የምሥራች ነው በተጨማሪም የተወሰኑ ኃጢአቶቹ ይራገፉለታል ሕፃናት በጀፃሃነምና በወላጆቻቸው መካከል የሚጋርዱ የሆኑ ጋሻዎች ናቸው ልጆቻችን አላህ ለእኛ የሰጠን በጣም ውድ የሆኑ ፃሃብቶቻችን ናቸው ስለሆነም ከሁሉም ዓይነት በተለይም ደግሞ ከመንፈሳዊ አደጋ ልንጠብቃቸው ግዴታ አለብን ይሁን እንጂ ልጆቻችንን ከተለያዩ አደጋዎች ልንጠብቃቸው የምንችለው እንዴት ነው። ሯወሯ ን አርሉም የትም ብትሆኑ ከእናንተ ጋር ነውአልሐዲድ በአውነቱ በሃቅ አላህን የሚፈራ ሰው ማለት የአልኢህሳንን እውነተኛ ትርጓሜ የተረዳና ይህንንም በሕይወቱ ላይ ተግባራዊ የሚያደርግ ነው የትም ሥፍራ ቢሆን በየትኛውም ጊዜ የሚሰራውንና ሁኔታውን የሚከታተለው መለኮታዊ ጥላ ከእርሱ እንደማይለይ አንድ ሰው አርግጠኛ ከሆነ ምንም ዓይነት ኃጢአት እያወቀ አይፈጽምም አላህ እንዲህ ይላል ሙ ሯ ህሠ አላህ በምድርም በሰማይም ምንም ነገር በአርሱ ላይ አይሰወርም አሊዒምራን ብዙውን ጊዜ ሰዎች በአለት ተአለት ኑራቸው ኃጢአት ከመፈፀም የሚቆጠቡት ሌሎች ሰዎች እንዳያዩዋቸውና ውርደት እንዳያገኛቸው በመፍራት ነው ታዲያ እንዲህ ዓይነቱ ሰው ሁሉን ቻይ የሆነው አላህን ለመፍራትና የሚሰራውንና የሚያደርጋትን እያንዳንዷን ድርጊት አርሱ እንደሚመለከተው ለማወቅ ይቀርባል። አላህ እንዲህ ይላል ። ለባለቤቴ ከዚህ ሌላ ልነግራት የምችለው ነገር አልነበረኝም አርግጥ ነው ተቆጣጣሪ ነበረኝ ያልኳት እርስዎን ሳይሆን አላህን ማለቴ ነበር ይህንንም ስል ለሰጠሁት አገልግሎት ምላሽ ለራሴ ምንም ነገር መውሰድ አልፈልግም ማለቴ ነው ዑመር ረዐ የሙዓዝን አባባል በሚገባ ተገነዘቡ በአርግጥም ለዚህ ዓለም ዛሃብት ደንታ እንደሌለው ያውቃሉ እናም ከራሳቸው ገንዘብ ላይ አንስተው ስጦታ ካበረከቱለት በኋላ እንዲህ አሉት ይህን ይዘህ ሂድና ለባለቤትህ ካበረከትክላት በኋላ አባብላት ሙአዝን ረዐ የመሰሉ ሰዎች የመጪው ዓለም መከራ እጀግ የሚያሳስባቸውና ነፍሳቸውንም በየጊዜው የሚመረምሩ ናቸው አላህንም በመጠንቀቅ ሙራቀባህ ሕይወታቸውን አገባድደዋል አላህ ሥራቸውን ይውደድላቸው በእዝነቱም ውስጥ ያስገባቸው ኡመር ረዐ እንዲህ ይሉ ነበር ከአላህ ፊት ቆማችሁ ሳይተሳሰባችሁ በፊት ከነፍሳችሁ ጋር ተሳሰቡ አቡ ሰኢድ አልኹድሪ ረዐ ባስተላለፉትና ሙስሊም በዘገቡት ሐዲስ ነብዩ ሰዐወ እንዲህ ብለዋል ዓለም ዱንያ አረንጓዴና ጣፋጭ ናት አላህ በዚህች ዓለም ላይ ተጠሪው ኸሊፋው አድርጓዓችኋል የምትሰሩትን ያያል በዓለማዊ መጠቀሚያ ዱንያ ውስጥ ተዘፍቃችሁ ከመማረክና ከሴቶች ጋር በሚኖራችሁ ግንኙነት ከሚፈጠረው እኩይ ተግባር ተጠንቀቁ አላህን ፍሩ የእስራኤል ልጆች የመጀመሪያ መፈተኛ ሴቶችን የሚመለከት ነበርና ስለሆነም ሁልጊዜም ቢሆን ጠንቃቃዎች ሆነን መገኘት ነው ያለብን በቀንም ሆነ በማታ የአላህን ውዴታ በሚያስገኙ መልካም ሥራዎች ራሳችንን ማስጠመድ ይኖርብናል ኸይር መልካም ሥራዎችን ሰርተን መጥገብ የለብንም እንደምናውቀው ዛያ አራት ሰዓት ሙሉ ኸይር መልካም ሥራን ለመሥራት ወቅቱ ክፍት ሆኖ ይጠብቃል መልካም ሥራ ማለት ገንዘብ ለተቸገሩ መመጽወት ወይም ምግብ ማብላት ብቻ የሚመስላቸው አይጠፉም የሚከተለውን ሐዲስ ስናነብ የመልካም ሥራ ዘርፎች ብዙ መሆናቸውንና የግድ የገንዘብ አቅም እንዲኖረን የሚጠይቁን አለመሆናቸውን እንገነዘባለን አቡ ሁረይራ ረዐ ባወሩትና ቡኻሪና ሙስሊም በዘገቡት ሐዲስ የአላህ መልክተኛ ሰዐወ እንደሚከተለው ብለዋል ሐይ በወጣችበት ቀን ሁሉ የማንኛውም ሰው መገጣጠሚያዎች ሰደቃ ምጽዋት ማቅረብ አለባቸው በሁለት ሰዎች መካከል በትክክል ብትፈርድ ሰደቃ ነው አንድን ሰው ከመጓጓዣው ላይ ብታወጣው ወይም እቃውን ብትጭንለት ሰደቃ ነው መልካም ንግግርም ሰደቃ ነው እያንዳንዲ ወደ ሶላት የምታመራ እርምጃ ሰደቃ ናት ከመንገድ ላይ ጐጂ ነገሮችን ማስወገድም ሰደቃ ነው እውነተኛ የአላህ ባሪያዎች የሰይጣን ተግዳሮት የማይበግራቸውና ምንጊዜም የጌታቸውን ውዴታ ለማግኘት ብቻ የሚሰሩ ናቸው ለእንዲህ አይነት ሰዎች አላህ ቀጥተኛ የሆነ መመራትንና እውቀትን ይሰጣቸዋል። ፌቓህ ርመን የከተማዋም ሰዎች ባመኑና በተጠነቀቁ ኖሮ በአነርሱ ላይ ከሰማይም ከምድርም በረከቶችን በከፈትንላቸው ነበር አል አዕራፍ ኢስላም የገንዘብ አቅም ባላቸው ተከታዮቹ ላይ ለድሆቻቸው የምትሰጥ የሆነችን ዘካ ግዴታ ሲያደርግ በፈቃደኝነትና የአላህን ውዴታ ፈልገው ገንዘባቸውን ለመልካም ሥራዎች ወጪ የሚያደርጉ ሰዎችንም በተለያዩ አጋጣሚዎች ማነሳሳቱን ገፋበት ምክንያቱም ሰዎች የአላህን አንድነት በልባቸው አምነው በምላሳቸው ካወጁ በላ የኃይማኖቱ ዋነኛ ግብ የሰው ልጅ ምድራዊ ሕይወት በተቻለ አቅም ሰላም የሰፈነባት እንዲሆን ማድረግ ነው እውነተኛ ሰላምና ፀጥታ የሚገኘው ደግሞ ከስግብግብነት የፀዱና የሌሎች ሰዎችን ምቾትና ደህንነት ከራሳቸው አስበልጠው የሚመኙ ሰዎች ሲፈልቁ ነው ይህም የአልኢህሳን ጽንሰፃሳብ እንጂ ሌላ አይደለም አዝነት ማለት በአንድ እውነተኛ ሙስሊም ልብ ውስጥ ምንጊዜም የሚነድ የፍቅር ነበልባል ነው አማኝ የሆነ ሰው ቸር ትሁትና ሌሎችን የሚያገለግል ቅንነት የተሞላ ፍጡር ነው አማኝ የሆነ ሰው በሌሎች ሰዎች ልብ ውስጥ ደስታና ሰላም እስከበራ ድረስ ማንኛውንም መስዋእትነት ለመክፈል የሚሰለፈው በፊት ለፊት ነው በሌላ በኩል ደግሞ አማኞች በማንኛውም አሳዛኝ ነገር ችግርና መከራ ወቅት ገንቢ የሆነ ሚናን በኅብረተሰቡ ውስጥ ይጫወታሉ ምንጊዜም የሚቆሙት ከግፉአኑ በሃዘን ከተደቆሱት ከተጣሉትና ከተረሱት ተስፋም ካጡት ጐን ነው የሰው ልጅ ሞራላዊ ብቃቶች የተሟሉ የሚሆኑት የቁርአንን አስተምህሮት ወደ ተግባር ሲቀይር ነው ለዚህም ነው የቁርአንን የመጀመሪያ ገጽ ስንገልጥ እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ የሚሉ ቃላትን የምናነበው የእኛ ጌታ አላህ ከሁሉም በላይ ሩህሩህና ከአዛኞች ሁሉ የበለጠ አዛኝ እንደሆነ ሲገልጽልን ይህን አዛኝ የመሆንን ባሕሪ አስከመጨረሻው ጥግ ድረስ ልናጐለብተው ይገባናል ማለት ነው አላህን ከልብ የማፍቀር ውጤት የሚንፀባረቀው ለፍጡራኑ ሩህሩህና አዛኝ በመሆን ነው የአላህ ወዳጅ የሆነ ሰው መስዋእት መክፈልን እንደ ዋነኛ የደስታ ምንጭ ይወስደዋል ስለሆነም ሶደቃ ምጽዋት ለአላህ ፍጡራን መስጠት እርሱን የማፍቀር መገለጫ ነው ማለት ነው እርግጥ ነው ብዙ የሶደቃ ምጽዋት አይነቶች አሉ። ብዙውን ጊዜ እኛ ሰዎች ስለ ምጽዋት ስናስብ ትዝ የሚለን ገንዘብ ወይም ምግብ ለተቸገሩት መስጠት ነው ሆኖም ግን የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ እንዲህ ብለዋል ሐይ በወጣችበት ቀን ሁሉ የማንኛውም ሰው መገጣጠሚያዎች ሶደቃ ምጽዋት ማቅረብ አለባቸው በሁለት ሰዎች መካከል በትክክል ብትፈርድ ሰደቃ ነው አንድን ሰው በመጓጓዣው ላይ ብታወጣው ወይም እቃውን ብትጭንለት ሰደቃ ነው መልካም ንግግር ሰደቃ ነው እያንዳንዷ ወደ ሶላት የምትመራ እርምጃ ሰደቃ ናት ከመንገድ ላይ ጐጂ ነገሮችን ማስወገድም ሰደቃ ነው የሰደቃ ምጽዋት የመጨረሻው ደረጃ ከራስ ይልቅ ለሌሎች ቅድሚያ የመስጠት ጽንሰ ፃሳብ የሚንፀባረቅበት አልኢአሳር ነው አልኢእሳርን ተግባራዊ የሚያደርጉት በእምነታቸው የበሰሉና ታላቅ ደረጃ ላይ የደረሱ ናቸው ስለሆነም እንዲህ ዓይነት ባሕሪን ለማንፀባረቅ የሚቻለው ጥሩ በሆነ ልብና ነፍስ ሲሆን እውነተኛ ኢእሣር ድህነትን አያስፈራም የአልኢሣር ከራስ ይልቅ ሌሎችን ማስቀደም በነብዩና በተከታዮቻቸው ዘመኖች ፈክቶ ነበር ማለት ይቻላል እርግጥ ነው ሁሉም በዚያ ዘመን የነበረ ሰው እንዲህ ዓይነቱን ባሕሪ ተላብሶ ነበር ማለት ትክክል ላይሆን ይችላል ሆኖም ግን ይህ ባህሪ በብዛትና በስፋት ይንፀባረቅ የነበረው በዚያ ወርቃማ ትውልድ ዘመናት መሆኑ እውነት ነው አቡ ሁረይራ ረዐ ባወሩት ሐዲስ አንድን ሰው የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ ከባለቤቶቻቸው ወደ አንዷ ምግብ ይኖራት እንደሆነ ጠይቆ እንዲመጣ ላኩት ሆኖም ግን ባለቤታቸው እርስዎን በላከዎት አላህ አምላለሁ ከውዛፃ በስተቀር ምንም የለኝም በማለት ገለፀች በዚህ ዓይነት ወደሌሎቹ ባለቤቶቻቸው ቢልኩም ሁሉም ተመሳሳይ መልስ ሰጧቸው ከዚያም ወደባልደረቦቻቸው ሄዱና ከእናንተ ማንኛችሁ ነው ይህን እንግዳየን የሚያስተናግድልኝ። መልሱ አዎን መሆኑን የተገነዘቡት ነቢይ ለአፍታም ሳያቅማሙ ውሰደው ሁሉም ያንተ ነው አሉት በዚህ ጊዜ ሰፍዋን ሸፃዳ በማለት ሙስሊም ሆነ ከዚያም እንዲህ አለ ይህን አይነት ችሮታ የምታደርግ ልብ የነቢይ ልብ እንጂ ሌላ አይደለችም ኢስላም ታሪኺ ከራስ ይልቅ ሌላውን ማስቀደም ኢሣር የቸርነት አንፀባራቂ ገጽታ ነው ልብንና መንፈስን በሚያጥለቀልቅ እንዲህ ዓይነት የፍቅር መገለጫ ድርጊት እጅጉን ደምቀው ይታዩበት የነበሩት የነብዩ ሰዐወ ባልደረቦችና ከአነርሱም በኋላ የመጡት ደጋግ ሰለፍ አባቶች ነበሩ በዚህ ድርጊታቸው የተነሳ ሌላው ቀርቶ በክህደታቸው ፀንተው የቆዩና እንደ አለት የጠጠረ ልብ የነበራቸው ሰዎች ወደ ኢስላም መግባት ችለዋል በተመሳሳይ ሁኔታ ከራስ ይልቅ የወንድምን ጉዳይ ማስቀደምን በአንክሮ ያስተዋሉ ጠላቶች ወዳጅ ሆነዋል የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ አንድን ነገር ተጠይቀው ከእርሳቸው ዘንድ እስካለ ድረስ አይሆንም ብለው አያውቁም በአንድ ወቅት ዘጠና ሺህ የሚሆን ዲርፃም ከእጃቸው ገብቶ ነበር ከምንጣፍ ላይ አደረጉትና የቸገረውና ገንዘብ ያስፈለገው ሁሉ እያነሳ አንዲወስድ አደረጉ የመልካም ሥራ ቢር ደረጃ የት ድረስ በቁርአን ቢር ተብሎ የሚጠራው በጐ ሥራ ልክ እንደ አልኢአሣር ሁሉ የምጡቅ ባህሪ መገለጫ ነው የሁሉም ምርጥ ባህሪያት ተምሳሌት የሆኑት ነብዩ ሰዐወ በዚህም ቢሆን አምሳያ አልነበራቸውም የሚከተለው ትረካ የሚያሳየን የአላህ መልእክተኛ በጣም ትንሽ በምትባል ነገር እንኳን ሳይቀር አንድም ቀን ከሌላው ይልቅ ነፍሳቸውን ከሌሎች አስቀድመው አንደማያውቁ ነው አንድ እለት ነብዩ ሰዐወ ሁለት ሲዋኮችን መፋቂያ አዘጋጁ አንደኛው የተስተካከለና እንከን የማይወጣለት ሲሆን ሌላኛው ደግም አባጣ ጐባጣ የሆነ ነበር ከዚያም የሚያምረውን ለአንዱ ባልደረባቸው በመስጠት እንደነገሩ የሆነውን ለራሳቸው አስቀሩ ባልደረባቸውም ሁኔታውን ካየ በጊላ ይኸኛው ይሻልዎታል የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ በማለት የሚያምረውን ሲዋክ እንዲወስዱ ጋበዛቸው የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ በዚህ ጊዜ እንዲህ አሉ አንድ ሰው ለአንድ ሰዓት እንኳን አብሮት ለቆየው ሰው የጓደኝነት ሃቁን ካጓደለበት መጠየቁ አይቀርም ኢህያእ ኡሉሙዲን የሚከተለው ትረካም ሌላው የዚህ ባህሪ መገለጫ ነው አንድ አለት የነብዩ ሰዐወ ባልደረቦች በመስጊድ ውስጥ ተሰባስበው የእርሳቸውን ኹጥባ ዲስኩር ያዳምጡ ነበር ከዚያም ነብዩ ሰዐወ የሚከተለውን የቁርአን አንቀጽ አነበቡ ዕሙ ቻአ ህን የምትወዱትን እስከምትለግሱ ድረስ በጐን ሥራ ዋጋውን አታገኙም ከምንም ነገር ብትለግሱ አላህ ያውቀዋል አሊዒምራን ባልደረቦቻቸው ነብዩ ሰዐወ ያነበቡትን የቁርአን አንቀጽ አዳምጠው የልባቸውን ሥር እስኪነዝራቸው ድረስ በጥልቀት እያስተነተኑና ስሜታቸው ተነክቶ ነበር ከሚወዱት ነገር ውስጥ ምን ቢሰጡ ለዚህ የቁርአን አንቀጽ ምላሽ እንደሚሆንላቸው በማሰብ ፀጥ ብለዋል ከዚያም በድንገት አንዱ ባልደረባቸው ተነሳ ይህ ሰው የአምነት ለዛ ውስጡን የቀየረው አቡ ጦልዛፃ ረዐ ነበር ስድስት መቶ የሚሆኑ የቴምር ዛፎችን ያቀፈና ለነብዩ ሰዐወ መስጊድ ቅርብ የሆነ ትልቅ የአትክልት ቦታ ነበረው ብዙ ጊዜ ነብዩ ሰዐወ ወደዚያ የአትክልት ሥፍራ እንዲመጡ ይጋብዛቸውና ዱአቸውን ያገኝ ነበር ከዚያም አቡ ጦልፃ እንዲህ አለ የአላህ መልእክተኛ ሆይ ካሉኝ ንብረቶች ሁሉ በጣም የምወደው ያን የሚያውቁትን የአትክልት ማሳየን ነው ከእንግዲህ አኔ ለአላህ ብዬ ለእርስዎ ሰጥቼዎታለሁ እርስዎ ለመሰለዎት ጉዳይ ሊያውሉት ይችላሉ ይህን ካለ በኋላ ውሳኔውን ተግባራዊ ለማድረግ ወደ አትክልት ሥፍራው ገሰገሰ እዚያ እንደደረሰም ባለቤቱ በዛፎቹ ጥላ ሥር ተቀምጣ አገኛት አቡ ጦልዛ ረዐ ወደ አትክልቱ ሥፍራ አልገባም በዚህ ጊዜ ባለቤቱ አቡ ጠልፃ ሆይ። መብላቱን ጠላችሁትም ሀሜቱንም ጥሉት አላህንም ፍሩ አላህ ፀፀትን ተቀባይ አዛኝ ነውና አልሑጁራት የሄ ዕ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ አንድ ሰው ስህተት ሲሰራ ከተመለከቱ ሰውየውን በቀጥታ አይጋፈጡትም ነበር ከዚያ ይልቅ ሁሉንም ሰዎች በመምከር ያም ሰው ጥፋቱን እንዲያርም እድል ይሰጡታል ይህም ልዝብና የሰውን ክብር ሳይነኩ የማስተማሪያ ምርጥ ዘዴ ነው በኃጢአትና በእኩይ ምግባር የተከበቡ ሙስሊሞችን ከገቡበት አዘቅት ለማውጣት መልካም ጠባይና ጥሩ አቀራረብን ማሳየት የአንድ ጥሩ ሙስሊም ባሕሪ ነው አንድ ጥሩ ሙስሊም ከዚህ አልፎ ለኃጢአተኞችና በወንጀል ለተጨማለቁ ሙስሊሞች አላህ ይምራቸው ዘንድ ዱዓ ፀሎት ያደርግላቸዋል የአላህ ነብይ ሰዐወ በዚህ ረገድ ታላቅ የሆነ ምሳሌ ትተውልን አልፈዋል የጧኢፍ ሰዎች በድንጋይ ሲወግራቸው አላህ አንዲቀጣቸው በመለመን ፈንታ ምህረትን ነበር የተመኙላቸው እርሳቸውንም ሆነ ተከታዮቻቸውን ለጉዳት የዳረጉ ሕዝቦችን አንዲያጠፋላቸው አንድም ጊዜ አላህን ለምነው አያውቁም የመካ ሰዎች ያን ያክል መከራቸውን ሲያበሏቸውና በመጨረሻም ሊገድሏቸው ሲሞክሩ እርሳቸው ግን አላህ እንዲምራቸው ይለምትኑላቸው ነበር በዚህ ልመናቸው ሰበብም ብዙ አምባገነኖችና ማን አለብኝ ባዮች ጥሩ ሙስሊም ለመሆን በቅተዋል ር እ ዎሙጳጵን ቼ መልካሚቱና ክፉይቱ ጠባይ አይስተካከሉም በዚያች እርሷ መልካም በሆነችው ጠባይ መጥፎይቱን ገፍትር ያን ጊዜ ያ በአንተና በርሱ መካከል ጠብ ያለው ሰው አርሱ ልክ እንደ አዛኝ ዘመድ ይሆናል ሐሚም አስሰጅዳህ ነብዩ ሰዐወ ሲናገሩ ጽድቅ ማለት መልካም ለሰራላችሁ በአፀፋው መልካም ማድረግ እንዲሁም መጥፎ ለሰራባችሁ መጥፎ ማድረግ ሳይሆን ለመጥፎ ሥራ መልካም ማድረግ ነውቡ ብለዋል ቲርሚዚ በሌላ በኩል ግን አንድ መታወቅ ያለበት ጉዳይ ኃጢአተኞችን በግለሰብ ደረጃ ብቻ ነው መታገስ የሚቻለው ሆኖም ግን ኃጢአታቸው ማህበረሰቡን የሚበክልና የቆመበትን ሥርአት የሚያፋልስ ሆኖ ሲገኝ በትእስግስት ሊታለፍ አይችልም በግለሰብ ደረጃ ኃጢአተኞችን በተመለከተ ግን ተደጋግሞ አንደተጠቀሰው መቻልና በመልካም ፀባይ መቅረብ ያስፈልጋል የአላህ መልእክተኛም ሰዐወ እንዲህ በማለት መክረዋል አግራሩ አንጅ አታጥብቁ ብስራት ነጋሪዎች አንጅ በታኞች አትሁኑ ቡኻሪ ምዕራፍ አሥራ ስድስት አላህንና መልእክተኛውን ሰዐወ መውደድ ፍቅር ማለት ደስታ ፍስፃሃ ሰላምና ፀጥታን በዚህች አላፊና ጠፊ ሕይወት ውስጥ ማጣጣም ማለት ነው ፍቅር ማለት የሕልውናችን ማቆያ የሆነው ህብስት እንዲጣፍጥ የሚያደርገው እርሾ ነው የማፍቀር ፀጋ ፈጣሪያችን አላህ ለሰው ልጆች ከሰጣቸው ፀጋዎች ሁሉ ታላቁ ነው። ሮ ሀፊ መመ ረውን ቃኃቃን መመን ኢርሥረ ሥ ሥ ቹ ች ዮነ ንዶ በላቸው አላህን የምትወዱ እንደሆናችሁ ተከተሉኝ አላህ ይወዳችልና ኃጢአቶቻችሁንም ይምርላችኋቷል አላህም መሐሪ አዛኝ ነው አሊዒምራን የማፍቀር ምልክቱ ለዚያ ላፈቀሩት ነገር ራስን ማስገዛትና መስዋእትነት መክፈል ነው አላህንና መልእክተኛውን ሰዐወ የሚወድ ሰው በልቡ ውስጥ ያለው ፍቅር ስራውን በቁርጠኛ ሐሳብ ንያ እና በፃቀኝነት እንዲከውን ያደርገዋል የሰው ልጅ የሚሰራቸው ማናቸውንም የአምልኮ ተግባራት በፍቅርና እየወደደ ቢሰራቸው ጠቀሜታቸው ታላቅ ይሆንለታል ከዚህ በተቃራኒ በልቡ ፍቅርና ውዴታ ሳይኖር እንዲሁ እየተሰላቸ የሚሰራቸው መልካም ተግባራት ጥንካሬ የሚጐድላቸው ቁርጠኛ ሐሳብ ንያ የሚያንሳቸውና ያልተስተካከሉ ይሆናሉ ሌላው ይቅርና ትንሽ ብትሆን እንኳን በጥሩ ንያና በፍቅር የምትሰራ ሥራ ባልተስተካከለ ንያ ከሚሰራ እጅግ ብዛት ያለው ሥራ ትበልጣለች አላህን የመውደድ ምልክትና ወደዚያው የሚያደርሰን መንገድ ግዴታ የተደረጉብንን የአምልኮ ተግባራት ከልብና በሙሉ ስሜት መከወን ነው ከዚያ በኋላ ደግሞ ነዋፊል ተጨማሪ የሆኑ መልካም ሥራዎችን ስንፈጽም አላህ አእየወደደንና ይበልጥ እያቀረበን ይመጣል በአንድ ሰው ልብ ውስጥ የአላህ ፍቅር እየጨመረ ሲመጣ ለአላህ ብሎ የሚሰራቸው መልካም ምግባራትም እንዲሁ የሚጨምሩ መሆኑ ጥርጥር የለውም ለዚህም ምክንያቱ በአላህ ፍቅር ልባቸው የነደደ ሰዎች ግዴታ የተደረጉባቸውን ነገሮች በመፈፀም ብቻ ስለማይረኩ ነው ከዚያ ይልቅ በተመሳሳይ ፍላጐትና ደስተኛ ስሜት ተጨማሪ የሆኑ መልካም ምግባራትን ይፈጽማሉ በውጤቱም ምድረበዳ የሆነ መሬት ውሃ እንደማይጠግበው ሁሉ እነርሱም በገ ምግባራትን ሰርተው አይጠግቡም በዚህ ሁኔታ ላይ ያሉ ሰዎችን ወደ አላህ መመለስ እንጂ ይበልጥ የሚያረካቸው ነገር የለም ሻን ያጸሽ። እርሳቸውም እንዲህ አሉ የወንድማችሁን የሁበይብን ሰላምታ ሁለቱን ምርኮኞች የመካ ከፃዲያን ብዙ ካሰቃዩአቸው በኋላ ገደሏቸው የታላቁ ሶፃባ የሁበይብ የመጨረሻ ቃል እንዲህ የሜል ነበር ሙስሊም ሰማእት ሸሂድ ሆኘ እስከተገደልኩ ድረስ በየትኛውም ዓይነት አኳኋን ብሞት ግድ የለኝም ቡኻሪ በተመሳሳይ ሁኔታ ለአላህ መልእክተኛ ሰዐወ በነበራቸው ጥልቅ ፍቅር የተነሳ ብዙ ወጣቶች እርሳቸውን የሚያስደስቱ ተግባራት በየጊዜው ለመፈጸም ይረባረቡ ነበር ከእነዚህ ወጣቶች ጥቂቶቹ ነብዩ ሰዐወ ለተለያዩ ነገሥታትና የፃገር መሪዎች የጻፏቸውን ደብዳቤዎች ለማድረስ ተራራ ዞረው ሸለቆና ምድረበዳ አቋርጠው ባህር ተሻግረው ፄደዋል ከዚያም በአምባገነን ነገሥታት ፊት በነፍሰ ገዳዮች ተከበው በታላቅ ወኔ የደብዳቤውን ፍሬ ሐሳብ አንብበዋል የነብዩ ሰዐወ ባልደረቦች ለእርሳቸው ከነበራቸው ፍቅርና አክብሮት የተነሳ መልካቸውና አቋማቸው ምን ዳንደሚመስል እንዲያብራሩ ሲጠየቁ መልስ ለመስጠት ይቸገሩ ነበር ኻሊድ ኢብን አልወሊድ ረዐ በአንድ ሙስሊም ጐሣ መኖሪያ አጠገብ ያልፍ ነበር የሩተሣው መሪ የነቢዩን ክብርና አጠቃላይ ሁኔታ አንዲገልጽለት ኻሊድን ረዐ ጠየቀው ኻሊድ ረዐ ሲመልስ እንዲህ አለ አኔ በአውነቱ የእርሳቸውን ሁኔታ መግለጽ አልችልም የጐሣው መሪ ጥያቄውን ገፋበት እባክህ የምታውቀውን ያክል አብራራልኝ ኻሊድ ረዐ እንዲህ አለ ልነግርህ የምችለው ነገር የአላህ መልእክተኛ ደረጃ ከፍተኛነት በላካቸው አካል ከፍተኛነት የሚለካ መሆኑን ነው አርሳቸውን የላካቸው የአጽናፈ ዓለሙ ፈጣሪ ነው ስለዚህ የእርሳቸውን ደረጃ በዚህ መገመት ትችላለህ ሌላው ታላቅ ሶፃባ አምር ኢብን አልአስ ረዐ ተመሳሳይ ጥያቄ ቀርቦለት እንደሚከተለው በማለት መልሳሷል እኔ ለእርሳቸዉ ካለኝ ክብር የተነሣ ቀና ብዬ በሙሉ ዓይኔ ተመልክቻቸው አላውቅም ስለሆነም ስለእርሳቸው ሁኔታ ልገልጽልህ አልችልም የነብዩ ሰዐወ ተከታዮች ለእርሳቸው የነበራቸውን ታላቅ ፍቅርና አክብሮት ከሜገልጹባቸው መንገዶች ዋነኛው እርሳቸው ያዘዙትን መፈጸምና የከለከሉትንም መከልከል ነው ከዚህ ቀጥሉ የሚቀርበውና ከአቡ አብዱራህማን አል ጁበሊ የተወራው ገጠመኝ ለዚህ አባባል እንደማሳያ ሆኖ ሊያገለግል ይችላል ከቤዛንታይን ወታደሮች ጋር በነበረን ጦርነት ከአቡ አዩብ አልአንሷሪ ረዐ ጋር በመሆን በመርከብ እንጓዝ ነበር መሪያችን አብደላህ ኢብን ቀይስ ነበር አቡ አዩብ አልአንሷሪ ረዐ ምርኮ የማከፋፈል ኃላፊነት ወደተሰጠው ሰው ሲመጡ አንድ የምታለቅስ ሴት ተመለከቱ ሴትዮዋ በጦርነቱ ጊዜ የተማረከች ነበረች አቡ አዩብ ረዐ ሴትዮዋ ለምን እንደምታለቅስ ሲጠይቁ ልጅ እንደነበራትና ልጅዋን ለይተው ለሌላ ሰው ድርሻ በማድረግ ስለሰጡባት መሆኑ ተነገራቸው አቡ አዩብ ረዐ ወዲያው ልጁን ፈልገው በማግኘት ለእናቱ መለሱላት ከዚያ በኋላ እናቱ ማልቀሷን አቆመች የምርኮ ክፍፍሉን ኃላፊነት የወሰደው ሰው በዚህ ጊዜ ወደ ጦሩ መሪ ወደ አብደላህ ኢብን ቀይስ ዐ በመሄድ አቡ አዩብ ረዐ ያደረጉትን ነገር ነገረው አብደላህ ለምን እንደዚያ እንዳደረጉ እንዲያስረዱት አቡ አዩብን ሲጠይቃቸው እንዲህ አሉ የአላህ መልእክተኛ ሰዐወ እናትና ልጅን የሚለያዩ ሰዎች አላህ በፍርዱ ቀን ከሚወዲቸው ሁሉ ይለያያቸዋል በማለት ሲናገሩ ሰምቻለሁ።

  • N.B. This Summary is Very Experimental!! based on the following scripts from:
    • https://github.com/millzon/textSummarizer-am
    • https://github.com/icoxfog417/awesome-text-summarization#motivation
Download Searchable PDF Download PDF

Comments:


memezon

Download options | Convert to Pdf | Book of the day

© dirzon | Terms of Service | Privacy | About | Services | Contact